በሀገር አቀፍ ደረጃ “በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በመካሄድ ላይ በሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በመላ ሀገሪቱ የሚገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲስትሪክት ጽ/ቤቶች እና ቅርንጫፎች እንዲሁም የዋናው መሥሪያ ቤት ሠራተኞች እና ኃላፊዎች ከ500 ሺ በላይ ችግኞችን ይተክላሉ፡፡
አገራዊ ዕቅዱን በሚገባ በመገንዘብ ወደተግባር ለመቀር ከባንኩ ሰራተኞች ብዙ ይጠበቃል ያሉት አቶ አቤ፤ የሥራ አመራሩ በእቅዱ ዙሪያ በቂ ግንዛቤ በመጨበጥ ለተግባራዊነቱ እንዲተጋ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሪፎርሙ ትግበራ በኋላ ያሳያውን ለውጥ አመርቂ መሆኑን ያነሱት አቶ አቤ በተገባደደው የበጀት ዓመት ብቻ የኢትዮጵያ ንግድ ለግሉ ዘርፍ የሰጠው ብድር ከ404 ቢልዮን ብር በላይ መሆኑን አስረድተዋል።