የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ ባንኩ ከሰሞኑ ገጥሞት ከነበረ ችግር ጋር በተያያዘ ለባንኩ ድጋፍ ላደረጉ አካለት በሙሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ፕሮፌሰር መሐመድ አብዱ እንዳሉት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሀገር የልማት እንቅስቃሴ ከፍተኛ እገዛ እያደረገ ያለ ባንክ ነው፡፡ባንኩ በሀገር ኢኮኖሚ ግንባታ ውስጥ የሚጠብቀበትን እየተወጣ እንዲቀጥል እና በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን ያስቀመጠውን ግብ ለማሳካት ይረዳው ዘንድ ደግሞ የባለድርሻ አካላት የፖሊሲን ጨምሮ ተገቢውን ድጋፍ ሊያደርጉለት እንደሚገባ ዋና ሰብሳቢው አሳስበው፣ ቋሚ ኮሚቴው አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል፡፡
በዛሬው እለት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንደገለፁት ባንኩ መጋቢት 6፣ 2016 ዓ.ም ሌሊት በተፈጠረ ችግር ምክንያት አላግባብ ከተወሰደበት 801,417,747.81 ብር ውስጥ 622.9 ሚሊዮን ብር (78 በመቶ) እስካሁን የተመለሰ ሲሆን ብር 168,609,283.7 ለመመለስ ቃል ተገብቷል፡፡ አቶ አቤ አላግባብ በ567 ግለሰቦች የተወሰደውን ቀሪ ብር 9,838,329.12 ለማስመለሰ ባንኩ ወደቀጣይ እርምጃዎች እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡