News Archive

24 Jul 2024

አቶ አቤ ሳኖ የ2016 ዓ.ም የአቢሲኒያ የኢንዱስትሪ ሽልማት የዳይመንድ ደረጃ ኒሻን እና ልዩ ዋንጫ ተረከቡ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ለባንኩ ትርፋማነትና ስኬታማነት ባሳዩት ብቃት ያለው አመራር የ2016 ዓ.ም. የዳይመንድ ደረጃ ኒሻን እና ዕውቅና ተበርክቶላቸዋል፡፡ በሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በመገኘት ዕውቅናውንና ሽልማቱን የተረከቡት የባንኩ የሰው ኃይል ም/ፕሬዚዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እና ሌሎችም የባንኩ ኃላፊዎች በፕሬዚዳንቱ ቢሮ በመገኘት ሽልማቱን ለአቶ አቤ ሳኖ አስረክበዋቸዋል፡፡

24 Jul 2024

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበርን ሕንጻ በጋራ ባለቤትነት ለማልማት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ተፈራረሙ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ በፊርማ ሥነ -ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ከ14.4 ቢሊየን ብር በላይ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኩል የሚሸፈን ሲሆን፤ ቀሪው 1.1 ቢሊየን ብር በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ይሸፈናል፡፡

24 Jul 2024

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአቢሲኒያ የኢንዱስትሪ ሽልማት ተሸላሚ ሆነ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በከፍተኛ አመራሮች ዘርፍ የዳይመንድ ደረጃ ኒሻን ተሸላሚ ሆነዋል፡፡

24 Jul 2024

የአቶ አቤ ምስጋና

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጠረ ችግር ምክንያት ያለአግባብ ተወስዶ የነበረውን ገንዘብ በማስመለስ ሂደት የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የባንኩ ሠራተኞች፣ ዲስትሪክቶች እና ቅርንጫፎች፣ የመንግስት አካላት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡