የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በበኩላቸው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በመስጠት 11 ስኬታማ ዓመታትን ያስቆጠረው የሲቢኢ ኑር አገልግሎት በደንበኞቹ ዘንድ ተአማኒነት በማትረፉ ውጤታማ ስለሆነ ለአጋርነታችሁ ምስጋና ይገባችሃል ብለዋል፡፡
ባቡል ኽይር የበጎ አድራጎት ድርጅት በቀን ከአራት ሺህ ስምንት መቶ በላይ አባወራዎችን የምገባ አገልግሎት ይሰጣል፡፡
በቀን ከ4800 በላይ አባወራዎችን የምገባ አገልግሎት እና ከ18 ሺህ በላይ የቤተሰብ አባላትን በያሉበት የምገባ አገልግሎት ለሚሰጠው ባቡል ኼይር የበጎ አድራጎት ድርጅት የ15 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገኘ::