የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ሀገራዊ እቅዱ እየተተገበረ ያለው በሪፎርም ማእቀፍ ውስጥ ከመሆኑ አንፃር እና ይህም ባንኩን በቀጥታ የሚመለከተው ከመሆኑ አንፃር በእቅድ አፈፃፀሙ ላይ ባንኩ ያለውን ድርሻ እና አበርክቶ እንዲሁም መልካም አጋጣሚ በሚገባ ተረድቶ ለቀጣይ ሥራ እንዲያግዝ ሪፖርቱ ላይ ውይይት ማድረግ ማስፈለጉን ገልፀዋል፡፡
የደምበኞቻችንን የውጪ ምንዛሪ ጥያቄ ለመመለስ እ.ኤ.አ እስከ 31/03/2025 ድረስ ባጠቃላይ በቁጥር 711 ደንበኞቻችን ያቀረቡትን ጥያቄዎች በሙሉ በመገምገም ከቀረቡት ጥያቄዎች ውስጥ ብዛታቸው 698(98%) ለሆኑ ደንበኞች በድምሩ የ122.5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድልድል የተደረገ መሆኑን እንገልጻለን።
አቶ አቤ በዲጂታል አማራጭ ባለፉት ስምንት ወራት አጠቃላይ ብር 3.9 ቢሊዮን ብድር ማቅረብ የተቻለ መሆኑን ገልፀው፣ በዚህም እስከ ፌብርዋሪ 28 ቀን 2025 ድረስ 717 ሺህ ደንበኞች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡