የሲቢኢ ኑር ፕሮዳክት ዴቨሎፕመንት እና ቢዝነስ ኤክስፓንሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዋር መሐመድ ደንበኞች ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን እንዲጠቀሙ ለማበረታታት የሽልማት መርሀ ግብሩ መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡
ባንኩ በረመዷን ፆም ወቅት ድጋፍ ማድረጉ ለማህበረሰቡ ያለውን ቅርበት እንደሚያሳይም ድጋፍ የተደረገላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በበኩላቸው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በመስጠት 11 ስኬታማ ዓመታትን ያስቆጠረው የሲቢኢ ኑር አገልግሎት በደንበኞቹ ዘንድ ተአማኒነት በማትረፉ ውጤታማ ስለሆነ ለአጋርነታችሁ ምስጋና ይገባችሃል ብለዋል፡፡