News Archive

04 Jul 2023

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሥራ አመራር አባላት በኬኒያ የልምድ ልውውጥ ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡

በኢትዮጵያ አስተማማኝ ዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚያግዝ በታለመው በዚህ የልምድ ልውውጥ ላይ በአቶ አቤ ሳኖ የሚመራ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ አመራር አባላት ልኡክ በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡

04 Jul 2023

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም በአጋርነት በቴሌብር ለህበረተሰቡ ተደራሽ የሚደርጉትን የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት አስጀመሩ፡፡

በሃገራችን ሁለንተናዊ የልማት እና የዕድገት ጉዞ ውስጥ ቀዳሚ ሚና በመጫወት ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም በአጋርነት፤ ዜጎች ዲጂታል የብድር እና የቁጠባ አገልግሎቶችን በቴሌብር እንዲያገኙ የሚያስችል የሞባይል የፋይናንስ አገልግሎት ሰኔ 20 ቀን 2015 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በተዘጋጀ መርሐ-ግብር በይፋ አስጀምረዋል፡፡ ሁለቱ ተቋማት በአጋርነት ያስጀመሩት አገልግሎት የባንክ እና የፋይናንስ አገልግሎትን ተደራሽነት እና ተጠቃሚነት ለማረጋግጥ የሚያስችል፣ ዜጎች ባሉበት ሆነው ፈጣን እና ቀላል በሆነ አማራጭ የፋይናንስ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡

03 Mar 2023

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ።

ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ እና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራአስኪያጅ አኑዋር ሱሳ ናቸው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ በስምምነቱ ወቅት እንደተናገሩት ባንኩ በቴሌኮም ዘርፍ አለም አቀፍ ልምድ ካለው ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት እድል በማግኘቱ መደሰታቸውን በመግለፅ ሁለቱ ትላልቅ ድርጅቶች በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ በመስራት በጋራ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያረጋግጡ ተናግረዋል።

13 Oct 2022

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስትራቴጂክ አጋርነት የተዘጋጀው 3ኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስትራቴጂክ አጋርነት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አዘጋጅነት በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበረው ሶስተኛው የሳይበር ደህንነት ወር መርሃ ግብር ጥቅምት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ተጀምሯል፡፡