News Archive

19 Apr 2025

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሀገራዊው የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ውይይት ተደረገ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ሀገራዊ እቅዱ እየተተገበረ ያለው በሪፎርም ማእቀፍ ውስጥ ከመሆኑ አንፃር እና ይህም ባንኩን በቀጥታ የሚመለከተው ከመሆኑ አንፃር በእቅድ አፈፃፀሙ ላይ ባንኩ ያለውን ድርሻ እና አበርክቶ እንዲሁም መልካም አጋጣሚ በሚገባ ተረድቶ ለቀጣይ ሥራ እንዲያግዝ ሪፖርቱ ላይ ውይይት ማድረግ ማስፈለጉን ገልፀዋል፡፡

05 Apr 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 122.5 ሚሊዮን ዶላር ለደንበኞቹ ድልድል አደረገ።

የደምበኞቻችንን የውጪ ምንዛሪ ጥያቄ ለመመለስ እ.ኤ.አ እስከ 31/03/2025 ድረስ ባጠቃላይ በቁጥር 711 ደንበኞቻችን ያቀረቡትን ጥያቄዎች በሙሉ በመገምገም ከቀረቡት ጥያቄዎች ውስጥ ብዛታቸው 698(98%) ለሆኑ ደንበኞች በድምሩ የ122.5 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድልድል የተደረገ መሆኑን እንገልጻለን።

04 Apr 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ 264.65 ቢልዮን ብር ብድር ለደንበኞቹ ማቅረቡ ተገለፀ።

አቶ አቤ በዲጂታል አማራጭ ባለፉት ስምንት ወራት አጠቃላይ ብር 3.9 ቢሊዮን ብድር ማቅረብ የተቻለ መሆኑን ገልፀው፣ በዚህም እስከ ፌብርዋሪ 28 ቀን 2025 ድረስ 717 ሺህ ደንበኞች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

04 Apr 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በባንክ ኢንዱስትሪው ውስጥ ያለውን የገበያ ድርሻ ማሳደጉ ተገለፀ፡፡

በፌብሩዋሪ 2025 መጨረሻ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘብ ብር 1.541 ትሪሊዮን፣ ጠቅላላ የብድርና የቦንድ ክምችት መጠን ብር 1.393 ትሪሊዮን፣ እንዲሁም አጠቃላይ ሃብት ብር 2.073 ትሪሊየን መድረሱን አቶ አቤ በሪፖርታቸው አመላክተዋል፡፡