አጭበርባሪዎች ሰሞኑን ከሲስተም ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን ችግር እንደ አጋጣሚ ለመጠቀም ሙከራ በማድረግ ላይ መሆናቸውን ደርሰንበታል፡፡ እነዚህ አጭበርባሪዎች በአብዛኛው ከባንክ የደወሉ በማስመሰል “የተዘጋ ሂሳብችሁን እንክፈትላችሁ” ፤ “ሂሳባችሁ እንዳይዘጋ የምንልክላቹሁን ኮድ አስገቡ” የሚል የማጭበርበሪያ ዘዴ በመጠቀም የዘረፋ ሙከራ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ ነገር ግን ባንካችን ስልክ ደውሎ ስለ ሂሳብዎ መረጃ የሚጠይቅበት፣ ሂሳብ የሚከፍትበትም ሆነ የሚዘጋበት አሰራር እንዲሁም ደንበኞች እንዲጠቀሙበት የሚልከው ምንም አይነት ኮድ የለም፡፡ በመሆኑም ማንኛውም የባንካችን ደንበኛ መሰል ሁኔታ ሲገጥመው ምንም አይነት እርምጃ ከመውሰድ በመቆጠብ በአቅራቢያ ወደሚገኝ ቅርንጫፍ በመሄድ አሊያም በ951 የባንኩ የደንበኞች ጥሪ ማዕከል በመደወል ስለሁኔታው መረጃ መጠየቅ እንዳለበት እናሳስባለን፡፡
ለውድ የባንካችን ደንበኞች የዲጂታል ባንክ አግልግሎት ሙሉ በሙሉ መጀመሩን እንገልፃለን። =============================== በሲስተም ችግር ምክንያት በባንኩ አገልግሎቶች ላይ ማለትም በቅርንጫፎች፥ በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሞ እንደነበር መግለፃችን ይታወቃል። በቅርንጫፍ እና በኤቲኤም የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀደም ብለው መጀመራቸውን ያሳወቅን ሲሆን አሁን ደግሞ በዲጂታል የሚሰጡ የባንክ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ መጀመራቸውን እናሳውቃለን። ውድ ደንበኞቻችን በትእግስት ስለጠበቃችሁን እያመሰገንን ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል በድጋሚ ይቅርታ እንጠይቃለን።
ክቡራን ደንበኞቻች፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቅርቡ በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ላይ የክፍያ ማስተካከያ ማድረጉ ይታወቃል። የተሻሻለውን የአገልግሎት ክፍያ በተመለከት ከደንበኞቻችን ባገኘነው ግብረ መልስ መሠረት በአንዳንድ አገልግሎቶች ላይ ድጋሚ የክፍያ ማሻሻያዎች አድርገናል፡፡ በድጋሚ ማሻሻያ የተደረገባቸው አገልግሎቶች እና የተሻሻለው ክፍያ በዚሁ ገጽ ላይhttps://combanketh.et/en/terms-and-tariff/ ያገኙታል።
Commercial Bank of Ethiopia would like to invite scholars, practitioners and other interested parties to submit papers that focus on Islamic finance and its integration within the Ethiopian financial, taxation and legal landscapes to be presented on a symposium on “Shaping the Modern Interest Free Banking Landscape in Ethiopia” scheduled in November, 2023 as part of the 10th Year Anniversary of its interest free banking service (CBE Noor) celebration. Please use the following link to get full information on the call for papers invitation: https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Call_for_Papers_4b01a86f9f.pdf
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲስ መስጠት የጀመራቸው የቁጠባ ሂሳብ አገልግሎቶች 1. እድሜያቸው ከ55 ዓመት በላይ የሆኑ የእድሜ ባለፀጎች የሚከፍቱት ‘ጋሻ የቁጠባ ሂሳብ’ (በሲቢኢ ኑር አገልግሎት ‘ቀዲም ሙዳራባህ የቁጠባ ሂሳብ‘ እና ‘ቀዲም ወዲዓህ የቁጠባ ሂሳብ‘)፣ 2. ደንበኞች ከውጭ ሀገራት የሚላክላቸውን ገንዘብ በባንኩ በመቀበል፣ ወይም በባንኩ የሚመነዝሩትን የውጭ ሀገር ገንዘብ የሚያስቀምጡበት ‘የውጭ ሐዋላ የቁጠባ ሂሳብ‘ ፣ 3. ደንበኞች ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ጉዞ ወጪ መሸፈኛ ገንዘብ የሚቆጥቡበት ‘ሲቢኢ ጉዞ የቁጠባ ሂሳብ‘ (በሲቢኢ ኑር አገልግሎት ‘ሲቢኢ ሪህላ ወዲዓህ የቁጠባ ሂሳብ‘ እና ‘ሲቢኢ ሪሕላ ሙዳራባህ የቁጠባ ሂሳብ‘) ናቸው፡፡ አገልግሎቶቹ ከመደበኛው ቁጠባ ሂሳብ ተጨማሪ ጥቅሞች እንዲኖራቸው ተደርገው የተዘጋጁ ናቸው፡፡ ደንበኞች የቁጠባ ሂሳቦቹን በመክፈት ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን ማግኘት ይችላሉ፡፡
CBE Noor is one of the full-fledged interest free banking services. Designed to comply with the central tenets of Sharia (or Islamic law) of doing business.
The core processes of the bank entrusted with the task of international banking services. The services are now provided at all branches of the bank with a single contact point of customer service relationship officers assigned for this purpose only.
Delivering banking services through high level of process automated machines and web-based. It provides easy, convenient, flexible and secure banking services for CBE customers using their digital cards, mobile phone, or internet accesses.
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጅታል የባንክ ሥርዓት በጊዜያዊነት መቋረጥን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰጠ መግለጫ ***** መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጅታል የባንክ ሥርዓት ላይ ባጋጠመ ችግር ምክንያት የባንኩ መደበኛ አገልግሎቶች ለተወሰኑ ሰዓታት መቋረጣቸዉ ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሪዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለፁት ባለፉት ስምንት ወራት በባንኩ ዲጂታል አገልግሎቶች በተከናወኑ ከ800 ሚሊዮን በላይ ግብይቶች ከ10 ትሪሊዮን በላይ የገንዘብ ዝውውር ተፈፅሟል፡፡ ይህም ከአጠቃላዩ የገንዘብ ዝውውር 73 በመቶ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞች ስጋት ሊገባቸው እንደማይገባ ገለፀ፡፡ የደንበኞች የግል ሂሳብ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰም፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሳይበር ጥቃት እንዳልደረሰበት ተገለፀ፡፡ • ባንኩ ጠንካራ የሳይበር ደህንነት ሥርዓት አለው ተብሏል፡፡
“ስኬታማ ምዕራፍ፤ ብሩህ ተስፋ” በሚል መሪ ቃል እየተከበረ የሚገኘው የሲቢኢ ኑር 10ኛ ዓመት ክብረ በዓል አንዱ አካል ሆኖ በተከታታይ የሚካሄደው የደንበኞች ምክክር መድረክ በዛሬው እለት (ህዳር 8፤ 2016) በአዲስ አበባ ከሚገኙ የሲቢኢ ኑር ደንበኞች ጋር በማካሄድ ተጀምሯል፡፡
ሰኔ 3 ቀን 2015 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በተካሄደ መርሃ ግብር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ በአባልነት ሲያገለገሉ የቆዩት አቶ ማሞ እስመለዓለም ምህረቱ፣ ዶ/ር አብርሃም በላይ እና አቶ ነብዩ ሳሙኤል የአገልግሎት ዘመናቸውን አጠናቀው የክብር ሽኝት ተደርጎላቸዋል፡፡ በዕለቱ ተሰናባች የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን ለተኩት ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ፣ ወ/ሮ ትዕግስት ሀሚድ እና አቶ ወንድምአገኘው ነገራ እንዲሁ የክብር አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡
Branchs
Customers
Partners
Transactions per Month