መንግስት የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ተወዳዳሪ እና ሳቢ ለማድረግ ገበያ መር የሆኑ ፖሊሲዎችን እና እስትራቴጂዎችን በመቅረጽ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል። ይህንንም ተከትሎ በባንክ ስራ ዘርፍ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ ሲሆን፤ የባንክ ኢንዱስትሪውም በአቅርቦት እና ፍላጎት ላይ የተመሰረተ የዋጋ ማሻሻያዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክም በገበያው ውስጥ ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲዘልቅና በሀገራችን የኢኮኖሚ ግንባታ ላይ ያለውን የጎላ ድርሻ አጎልብቶ መዝለቅ ይችል ዘንድ ለደንበኞቹ የሚሰጠውን አገልግሎት ቀልጣፋ ለማድረግ በርካታ የትራንስፎርሜሽን ስራዎችን እያከናወነ ከመሆኑም በተጨማሪ የደንበኞችን ፍላጎት መሰረት ያደረጉ አዳዲስ አማራጭ የብድር አገልግሎቶችን ለማስጀመር በሂደት ላይ ይገኛል። ይሁንና ባንካችን እየተገበረው ያለው ሪፎርም አጠቃላይ የኦፕሬሽንና የአስተዳደር ወጪ እድገትን በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ ያስቻለው ቢሆንም በተለያየ ምክንያት እየተከሰተ ያለው አጠቃላይ የቁጠባ ማሰባሰቢያ ወጪ ከፍተኛ መሆንና ባንካችን ለሚሰጠው የብድር አገልግሎት የሚያስከፍለው የወለድ ምጣኔ በገበያ ላይ ከሚታየው የወለድ ምጣኔ አንጻር ሲታይ በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ በባንካችን ዘላቂ ትርፋማነት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ፈጥሯል። ስለሆነም ይህንን ለማስተካከልና ባንካችንን በፋይናንስ ዘርፉ የሚገባውን ሚና እንዲጫወት ለማስቻል ለሚሰጠው የብድር አገልግሎት ወጪውን ታሳቢ ያደረገ መጠነኛ የብድር ወለድ ምጣኔ ማሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። ነገር ግን የግብርና ዘርፍን ከማበረታታት አንፃር የወለድ ምጣኔው የተቀነሰ ሲሆን፤ የሕብረተሰቡን የመክፈል አቅም ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ለኮንዶሚኒየም መኖሪያ ቤቶች ብድር የሚከፈለው የወለድ መጠን ባለበት እንዲቀጥል ተወሰኗል። በመንግስትና በግል ድርጅት ተበዳሪዎች መካከል የነበረው የምጣኔ ልዩነትም ተስተካክሏል፡፡ በዚህም መሰረት እ.ኤ.አ. ከማርች 7 ቀን 2025 ጀምሮ ባንካችን የዋጋ ማሻሻያውን ተግባራዊ እንደሚያደርግ እያስታወቅን የተደረገው የዋጋ ማሻሻያ ዝርዝር ከዚህ በታች ባለው ሰንጠረዥ ተመላክቷል። https://combanketh.et/cbeapi/uploads/Lending_Rate_Change_be8c8d4bfc.pdf
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተደራሽነቱን ከሀገር ውጭ ማስፋት እንዳለበት ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) የባንኩን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ገምግሟል፡፡
ትላንት ለገንዘብዎ ሁነኛ ባላደራ ሲፈልጉ በመላው ሀገራችን ቅርንጫፎቹን በመክፈት እርስዎ ወዳሉበት የደረሰው ባንካችን፣ ዛሬም በፈጣን እንቅስቃሴ ላይ ባለችው ዓለማችን፤ ከዘመኑ ጋር እየዘመነ አማራጮችዎን እያሰፋና ፍላጎትዎን እያሟላ በተለመደው ትጋቱ ቀጥሏል! ትጋት እና ጥረታችን ግብ መምታት ስኬቱ የሚለካው በርስዎ እርካታና ደስታ ነውና ለዚህ እውነት ቃላችንን ልናድስ "የላቀ አገልግሎት ደስተኛ ደንበኛ" በሚል መሪ ቃል የደንበኞች አገልግሎት ወርን እናከብራለን፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለዘመናት በአብሮነት ለዘለቃችሁ ክቡራን ደንበኞቹ ምስጋናውን እያቀረበ ከታህሳስ 24 እስከ ጥር 25 የሚከበረው የደንበኞች አገልግሎት ወር የናንተ ነውና አብራችሁን እንድትሆኑ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን። ከዚሁ ክብረ በዓል ጋር ተያይዞ የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የጉዞ ሂደት የሚያሳይ አውደ-ርዕይ እና አዲሱን የዋና መሥሪያ ቤት ህንፃ ከታህሳስ 24 እስከ ታህሳስ 30 በዋና መሥሪያ ቤታችን ተገኝተው እንዲጎበኙ ተጋብዘዋል።
ምዝገባው ታህሳስ 15 /December 24, 2024/ ይጠናቀቃል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የስያሜ ስፖንሰር የሆነበት ነጋድራስ የሥራ ፈጠራ ውድድር በየዙሩ 1.8 ሚልዮን ብር እንዲሁም ለአሸናፊዎች አሸናፊ 5 ሚሊዮን ብር ሽልማት፤ ምርጥ አምስት ዉስጥ ለሚገቡ ተወዳዳሪዎች ደግሞ ያለማስያዣ የብድር እድል ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሚያገኙበት የምእራፍ አራት ምዝገባ ሊጠናቀቅ ሁለት ሳምንት ብቻ ይቀራል፡፡ የሥራ ሀሳብዎን ወደ ነጋድራስ በማምጣትዎ ስራዎን ያስተዋዉቃሉ፤ ከአንጋፋ ዳኞች ጠቃሚ ምክር ያገኛሉ ፤ ያለማስያዣ የብድር ዕድል ተጠቃሚ ይሆናሉ ፡፡ ለመመዝገብ ሊንኩን (https://ebc.et/NegadrasRegistration.aspx) ይጠቀሙ፡፡ ይመዝገቡ ፤ ይወዳደሩ፤ ይሸለሙ!
ለክቡራን የባንካችን ደንበኞች ***** ባንካችን የአገልግሎት ክፍያ ማሻሻያ በሚያደርግበት ወቅት ለክቡራን ደንበኞቹ ቀደም ብሎ እንደሚያሳውቅ ይታወቃል። በዚህ መሠረት ባንካችን በሚሰጣቸው የብድር፣ የቅርንጫፍ እና የዲጂታል፣ እንዲሁም በዓለም አቀፍ የባንክ አገልግሎቶች ላይ በቅርቡ የብድር ወለድ እና የአገልግሎት ዋጋ ማሻሻያ የሚያደርግ መሆኑን ለክቡራን ደንበኞቻችን እናሳውቃለን። ******* የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!
CBE Noor is one of the full-fledged interest free banking services. Designed to comply with the central tenets of Sharia (or Islamic law) of doing business.
The core processes of the bank entrusted with the task of international banking services. The services are now provided at all branches of the bank with a single contact point of customer service relationship officers assigned for this purpose only.
Delivering banking services through high level of process automated machines and web-based. It provides easy, convenient, flexible and secure banking services for CBE customers using their digital cards, mobile phone, or internet accesses.
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በበኩላቸው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በመስጠት 11 ስኬታማ ዓመታትን ያስቆጠረው የሲቢኢ ኑር አገልግሎት በደንበኞቹ ዘንድ ተአማኒነት በማትረፉ ውጤታማ ስለሆነ ለአጋርነታችሁ ምስጋና ይገባችሃል ብለዋል፡፡
ባቡል ኽይር የበጎ አድራጎት ድርጅት በቀን ከአራት ሺህ ስምንት መቶ በላይ አባወራዎችን የምገባ አገልግሎት ይሰጣል፡፡
በቀን ከ4800 በላይ አባወራዎችን የምገባ አገልግሎት እና ከ18 ሺህ በላይ የቤተሰብ አባላትን በያሉበት የምገባ አገልግሎት ለሚሰጠው ባቡል ኼይር የበጎ አድራጎት ድርጅት የ15 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አገኘ::
የነጋድራስ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ፈጠራ ውድድር አሸናፊ በመሆን አብርሃም እና አብዲ በኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክል ፈጠራ ሥራ በማቅረብ አሸናፊ ሆነዋል።
ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች እና ማኔጅመንት አባላት የተሰበሰበ 18 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ባንኩ 12 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ በድምሩ 30 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለእያንዳዳቸው 10 ሚሊዮን ብር ብድር ያለማስያዣ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
Branchs
Customers
Partners
Transactions per Month