03 Mar 2023
ስምምነቱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ እና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራአስኪያጅ አኑዋር ሱሳ ናቸው። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ በስምምነቱ ወቅት እንደተናገሩት ባንኩ በቴሌኮም ዘርፍ አለም አቀፍ ልምድ ካለው ድርጅት ጋር በጋራ ለመስራት እድል በማግኘቱ መደሰታቸውን በመግለፅ ሁለቱ ትላልቅ ድርጅቶች በስትራቴጂክ ጉዳዮች ላይ በመስራት በጋራ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያረጋግጡ ተናግረዋል።
13 Oct 2022
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ስትራቴጂክ አጋርነት እና በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አዘጋጅነት በተለያዩ ዝግጅቶች የሚከበረው ሶስተኛው የሳይበር ደህንነት ወር መርሃ ግብር ጥቅምት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ተጀምሯል፡፡
05 Oct 2022
አፍሪካን ቢዝነስ ባወጣው መረጃ መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ2022 ባስመዘገበው አፈፃፀም በ929 ሚሊዮን ዶላር ካፒታል ከምስራቅ አፍሪካ ባንኮች መካከል በ3ኛ ደረጃ ተቀምጧል፡፡
05 Oct 2022
ይህ የተገለፀው ባንኩ በፕላቲኒየም ደረጃ ስፖንሰር ያደረገው የኢሬቻ ክብረ በዓል አካል በሆነውና በስካይላይት ሆቴል በተከናወነው 2ኛው የቱሪዝም ሽልማት እና የሚስ ቱሪዝም ኦሮሚያ የቁንጅና ውድድር ዝግጅት ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሱራ ሳቀታ በዝግጅቱ ላይ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኦሮሞ ሕዝብ ታላቅ የምስጋና በዓል የሆነው ኢሬቻ የ2015 ዓ.ም ክብረ በዓል አካል በመሆኑ ታላቅ ክብር ተሰምቶታል፡፡