News Archive

14 Jul 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፈው በጀት ዓመት ከ458.5 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሉንም ዜጋ የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ እያደረገ ከሚገኘው ጥረት ጋር በተያያዘ ከ9.1 ቢሊዮን ብር በላይ በዲጂታል አማራጮች ብድር የሰጠ ሲሆን፣ 5.8 ቢሊዮን ብር በቴሌ ብር እንዲሁም 3.3 ቢሊዮን ብር በሲቢኢ ብር አገልግሎት ብድር መሰጠቱን ከቀረበው ሪፖርት ለመረዳት ተችሏል።

14 Jul 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፈው በጀት ዓመት የሰበሰበው ተቀማጭ ገንዘብ በ77 ዓመት ካሳካው የበለጠ መሆኑ ተገለፀ።

በቀረበው የዓመቱ የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ እንደተገለፀው፣ የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘብ 1.69 ትሪሊዮን ብር ደርሷል። ይህም ከአምና ተመሳሳይ ወቅት አፈፃፀም የ43.9 በመቶ እድገት ያለው ነው።

10 Jul 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሁሉም የሥራ አፈፃፀም መለኪያዎች የገበያ ድርሻውን ማሳደጉ ተገለፀ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ዛሬ በተጀመረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2017 (2024/25) በጀት ዓመት ዓመታዊ ጉባኤ ላይ እንደተናገሩት ባንኩ ባለፈው በጀት ዓመት አመርቂ የሥራ አፈፃፀም ያስመዘገበ ሲሆን፣ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜም በሁሉም የሥራ አፈፃፀም መለኪያዎች የገበያ ድርሻውን ማሳደግ ችሏል።

10 Jul 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2017 (2024/25) በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም የሚገመግምበትን እና የቀጣይ አምስት ዓመት ስትራቴጂክ እቅድ ሥራ የሚያስጀምርበትን ዓመታዊ ጉባኤ በማካሄድ ላይ ነው።

የባንኩ የሥራ አመራ ቦርድ አባላት፣ የዋናው መሥሪያ ቤት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሪጅን እና የዲስትሪክቶች የሥራ ኃላፊዎች እና ከመላው ሀገሪቱ የመጡ የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጆች በጉባኤው ታድመዋል።