News Archive

28 Feb 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጠቃላይ ተቀማጭ 1.54 ትሪሊዮን ብር ደረሰ።

አቶ አቤ አጠቃላይ በባንኩ ከተፈጸሙ የገንዘብ ግብይቶች 84.5 በመቶ የሚሆነው በዲጂታል የክፍያ አማራጮች የተፈጸሙ መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም አበረታች እንደሆነና የአገልግሎት ጥራቱንም ይበልጥ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

26 Feb 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተደራሽነቱን ከሀገር ውጭ ማስፋት እንዳለበት ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) የባንኩን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ገምግሟል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተደራሽነቱን ከሀገር ውጭ ማስፋት እንዳለበት ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) የባንኩን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ገምግሟል፡፡ ************************** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት ገምግመዋል፡፡ በግምገማው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፣ በተቀማጭ ገንዘብ አሰባሰብ የተመዘገበው ውጤት አበረታች መሆኑ እና በዚህ እረገድ የገበያ ድርሻውን ማሳደግ መቻሉ ታይቷል፡፡

25 Feb 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሀገራቸን ዘመናዊ የዘካ አከፋፈል ሥርዓት በማስተዋወቅ ጉልህ ሚና እንዳለው ተገለፀ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲቢኢ ኑር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኑሪ ሁሴን እንዳሉት፤ ባንካችን ከዘካ ክፍያና አሰባሰብ ሥርዓት ጋር በተያያዘ የከፋዮችን እና የተቀባዮችን ጊዜ፣ ጉልበትና ገንዘብ ብክነትን የሚያስቀር ፤ በዘመናዊ የባንክ አሠራር የተደገፈና ሚስጢራዊነቱን የጠበቀ፤ የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት ለደንበኞቹ በማቅረብ ፤በሀገራችን ፈር ቀዳጅ ነው::

25 Feb 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎትን በማሳደግ በአምስት ዘርፎች ሽልማት አገኘ፡፡

በመርሀ ግብሩ ላይ በመገኘት ባንኩ ያገኛቸውን ሽልማቶች የተቀበሉት የሲቢኢ ኑር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኑሪ ሁሴን እንዳሉት ከአምስቱ ሽልማቶች ሁለቱ የባንኩ የሥራ መሪዎች በግለሰብ ደረጃ ለዘርፉ ላደረጉት አስተዋፅኦ እውቅና የተሰጠባቸው ናቸው፡፡