10 Mar 2025
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሻሸመኔ ዲስትሪክ ዳይሬክተር አቶ ደዋኖ ሁሴን በመርሐ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት ባንኩ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከሚያደርገው ጥረት ጋር ተያይዞ በረመዷን ወር ለሙስሊሙ ማህበረሰብ አብሮነቱን ለማሳየት የማዕድ ማጋራቱ መከናወኑን ገልፀዋል።
10 Mar 2025
ድጋፉን በራሳቸው እና በኮሜርሻል ኖሚኒስ ስም ያስረከቡት የኮሜሪሻል ኖሚኒስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ መቄዶንያ ለሚሠራው የበጎ አድራጎት ሥራ ያላቸውን አድናቆት ገልፀው፣ በቀጣይም አቅም በፈቀደ ሁሉ እገዛ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡
28 Feb 2025
አቶ አቤ አጠቃላይ በባንኩ ከተፈጸሙ የገንዘብ ግብይቶች 84.5 በመቶ የሚሆነው በዲጂታል የክፍያ አማራጮች የተፈጸሙ መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም አበረታች እንደሆነና የአገልግሎት ጥራቱንም ይበልጥ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
26 Feb 2025
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተደራሽነቱን ከሀገር ውጭ ማስፋት እንዳለበት ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) የባንኩን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ገምግሟል፡፡ ************************** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት ገምግመዋል፡፡ በግምገማው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፣ በተቀማጭ ገንዘብ አሰባሰብ የተመዘገበው ውጤት አበረታች መሆኑ እና በዚህ እረገድ የገበያ ድርሻውን ማሳደግ መቻሉ ታይቷል፡፡