News Archive

10 Mar 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲቢኢ ኑር የ1446ኛው ዓ.ሒ የረመዷን ፆምን ምክንያት በማድረግ በሻሸመኔ ከተማ ገቢና አጋዥ ለሌላቸው ሙስሊም የህበረተሰብ ክፍሎች ማዕድ አጋራ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሻሸመኔ ዲስትሪክ ዳይሬክተር አቶ ደዋኖ ሁሴን በመርሐ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት ባንኩ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከሚያደርገው ጥረት ጋር ተያይዞ በረመዷን ወር ለሙስሊሙ ማህበረሰብ አብሮነቱን ለማሳየት የማዕድ ማጋራቱ መከናወኑን ገልፀዋል።

10 Mar 2025

ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የ 3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ!

ድጋፉን በራሳቸው እና በኮሜርሻል ኖሚኒስ ስም ያስረከቡት የኮሜሪሻል ኖሚኒስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ መቄዶንያ ለሚሠራው የበጎ አድራጎት ሥራ ያላቸውን አድናቆት ገልፀው፣ በቀጣይም አቅም በፈቀደ ሁሉ እገዛ ለማድረግ ቃል ገብተዋል፡፡

28 Feb 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አጠቃላይ ተቀማጭ 1.54 ትሪሊዮን ብር ደረሰ።

አቶ አቤ አጠቃላይ በባንኩ ከተፈጸሙ የገንዘብ ግብይቶች 84.5 በመቶ የሚሆነው በዲጂታል የክፍያ አማራጮች የተፈጸሙ መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም አበረታች እንደሆነና የአገልግሎት ጥራቱንም ይበልጥ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቶት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

26 Feb 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተደራሽነቱን ከሀገር ውጭ ማስፋት እንዳለበት ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) የባንኩን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ገምግሟል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተደራሽነቱን ከሀገር ውጭ ማስፋት እንዳለበት ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) የባንኩን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ገምግሟል፡፡ ************************** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት ገምግመዋል፡፡ በግምገማው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፣ በተቀማጭ ገንዘብ አሰባሰብ የተመዘገበው ውጤት አበረታች መሆኑ እና በዚህ እረገድ የገበያ ድርሻውን ማሳደግ መቻሉ ታይቷል፡፡