News Archive

04 Jan 2025

ለ አንድ ወር ከሚቆየው የደንበኞች አገልግሎት ወር ጋር ተያይዞ በወጭ ንግድ ከተሰማሩ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡

የብድር ማስያዣ ንብረት ግምት፣ የብድር አሰጣጥ ሂደት፣ ለወጭ ንግድ የሚሰጡ አገልግሎቶች፣ የሲቢኢ ኑር አገልግሎት፣ የአገልግሎት ክፍያ እና ሌሎችም በውይይቱ ትልቅ ትኩረት ያገኙ ጉዳዮች ነበሩ፡፡

04 Jan 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዘላቂ ስኬት የተመሠረተው በደንበኞች እርካታ ላይ መሆኑ ተገለፀ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካስተመር ኤክስፔሪያንስ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለየሱስ በቀለ በቀጣይ የደንበኞች አገልግሎት ወር ከአለም አቀፍ የደንበኞች አገልግሎት ሳምንት ጋር በማስተሳሰር በየዓመቱ በጥቅምት ወር በተጠናከረ ሁኔታ በባንኩ እንደሚከበር ገልፀዋል፡፡

04 Jan 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በደንበኞች አገልግሎት ወር መክፈቻ መርሐ ግብር ላይ ለደንበኞች ያስተላለፉት መልዕክት፡፡

የባንካችን ደንበኞች ብቻ ሳትሆኑ ቤተሰብም በመሆናችሁ ስለአገልግሎት አሰጣጣችን የምትሰጡንን ሀሳብ እና አስተያየት አክብረን እንቀበላልን፡፡ ለተግባራዊነቱም አበክረን እንሠራለን፡፡ የሚያጋጥሙንን ተግዳሮቶች ከናንተ ከደንበኞቻችን ጋር በመሆን ወደምቹ አጋጣሚ እየቀየርን እድገታችንን እናስቀጥላለን፡፡

04 Jan 2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞች አገልግሎት ወርን ማክበር ጀመረ፡፡

የኢፌዲሪ የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር እና የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ባንኩ ፈተናዎችን አልፎ ዛሬ ለደረሰበት ስኬት የደንበኞች አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው፣ “እምነታችሁን ስለሰጣችሁን እና ከባንካችን ጋር ስለምትሠሩ እናመሰግናለን’’ በማለት ለባንኩ ደንበኞች መልእክት አስተላልፈዋል፡፡