26 Feb 2025
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተደራሽነቱን ከሀገር ውጭ ማስፋት እንዳለበት ተገለፀ፡፡ የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) የባንኩን የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ገምግሟል፡፡ ************************** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ የሥራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት ገምግመዋል፡፡ በግምገማው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የግማሽ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፣ በተቀማጭ ገንዘብ አሰባሰብ የተመዘገበው ውጤት አበረታች መሆኑ እና በዚህ እረገድ የገበያ ድርሻውን ማሳደግ መቻሉ ታይቷል፡፡
25 Feb 2025
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሲቢኢ ኑር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኑሪ ሁሴን እንዳሉት፤ ባንካችን ከዘካ ክፍያና አሰባሰብ ሥርዓት ጋር በተያያዘ የከፋዮችን እና የተቀባዮችን ጊዜ፣ ጉልበትና ገንዘብ ብክነትን የሚያስቀር ፤ በዘመናዊ የባንክ አሠራር የተደገፈና ሚስጢራዊነቱን የጠበቀ፤ የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት ለደንበኞቹ በማቅረብ ፤በሀገራችን ፈር ቀዳጅ ነው::
25 Feb 2025
በመርሀ ግብሩ ላይ በመገኘት ባንኩ ያገኛቸውን ሽልማቶች የተቀበሉት የሲቢኢ ኑር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኑሪ ሁሴን እንዳሉት ከአምስቱ ሽልማቶች ሁለቱ የባንኩ የሥራ መሪዎች በግለሰብ ደረጃ ለዘርፉ ላደረጉት አስተዋፅኦ እውቅና የተሰጠባቸው ናቸው፡፡
04 Feb 2025
በጀት ዓመቱ አጋማሽ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች በተከናወኑ እና በቁጥር ከ910 ሚሊዮን በላይ በሚደርሱ ግብይቶች ከ5.4 ትሪሊዮን ብር በላይ የሚደርስ የገንዘብ እንቅስቃሴ ተከናውኗል፡፡