News Archive

27 Dec 2024

የሲቢኢ ብር ፕላስ ገና ባዛር በደማቅ ሥነ- ሥርዓት ተከፈተ::

እስከ ገና ዋዜማ ድረስ በሚቆየው የሲቢኢ ብር ፕላስ ገና ባዛር ከ400 በላይ የንግድ ድርጅቶችና እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እየተሳተፉበት ይገኛል፡፡

23 Dec 2024

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በፋስት ፔይ ዓለም አቀፍ የገንዘብ መላኪያ መተግበሪያ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡

በኢትዮጵያውያን ሥራ ፈጣሪዎች የበለፀገው ይህ የገንዘብ መላኪያ መተግበሪያ ከውጭ ሀገራት በማንኛውም ቦታ እና ሰዓት በፍጥነት በአንድ ጊዜ እስከ 10 ሺ ዶላር ወደ ተጠቃሚ ሂሳብ በነፃ መላክ የሚያስችል እንደሆነ የፋስት ፔይ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍፁም ተስፋዬ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ተናግረዋል፡፡

23 Dec 2024

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የአዳማ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት በጋራ መሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

ይህ ስምምነት በአዳማ ከተማ የሚገኙ ደንበኞች ወርሀዊ የውሀ ፍጆታ ክያቸውን በሲቢኢ ብር ለመፈፀም የሚያስችላቸው ሲሆን፣ ይህም በከተማው ዲጂታል የክፍያ ሥርዓትን ለማስፋፋት የተያዘው ዕቅድ አካል መሆኑ ተገልጿል።

23 Dec 2024

በአሶሳ ከተማ እና አካባቢው ከሚገኙ የሲቢኢ ኑር ደንበኞች ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡

ባንኩ የሚሰጠው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሸሪዓ መርሆዎችን የተከተለ ስለመሆኑ በማብራሪያ ወቅት የተገለፀ ሲሆን፣ የብድር አገልግሎትን ጨምሮ ደንበኞች ያነሷቸው ሌሎች ጉዳዮች በባንኩ አሠራር መሠረት ምላሽ እንደሚያገኙ ተብራርቷል፡፡