አቶ ኃይለየሱስ የደንበኞች አገልግሎት ወር በተለያዩ ዝግጅቶች መከበሩን አስታውሰው፣ ሁነቱ ባንኩ ከደንበኞቹ ጋር ይበልጥ የተቀራረበበት፣ ለደንበኞች ያለውን ክብር የገለፀበት እና በቀጣይ ሊያሻሽላቸው ስለሚገቡ ጉዳዮችም ግብአት ያገኘበት መሆኑንም ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አትሌቲክስ ቡድንለሽልማት ከተዘጋጁ ሦስት ዋንጫዎች ሁለቱን ያሸነፈ ሲሆን፣ 12 የወርቅ ፣11 የብር እና 13 የነሀስ ሜዳሊያዎች በማምጣት ከፍተኛ ድል መቀዳጀት ተችሏል፡፡
ቀደም ብሎ ሻምፒዮነቱን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን እሁድ ግንቦት 3 ቀን 2017 በሀዋሳ አርቴፊሻል ሜዳ ባካሄደው የመጨረሻ ሳምንት መርሀ ግብር ጨዋታ አዳማ ከተማን 5 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በማሸነፍ በ62 ነጥብ ዋንጫውን አንስቷል።