ማሳወቂያ

የውጭ ሀገር የምንዛሪ ተመን

May 2nd 2024

ገንዘብ የገንዘብ መግዣ ዋጋ የገንዘብ መሸጫ ዋጋ

ምርት እና አገልግሎት

በእጅ ስልክ የሚፈጸም የባንክ አገልግሎት

ዝርዝር ይመልከቱ

የሲቢኢ ብር

ዝርዝር ይመልከቱ

በካርድ የሚፈጸም የባንክ አገልግሎት

ዝርዝር ይመልከቱ
ሲቢ ኑር

ሲቢ ኑር

ሲቢ ኑር ወለድ አልባ የባንክ አገልግሎት ሲሆን በመደበኛው የባንክ አገልግሎቶች ላይ በፍላጎትም ዪሁን በሀይማኖት ምክንያት አገልግሎቱን ማግኝት ላልቻሉ የሕብረተሰብ ክፍሎች የቀረበ ሁሉን አቀፍ የባን አገልግሎት ነው፡፡ ይህም አገልግሎት የተመሰረተው በሸሪያ የንግድ እንቅስቃሴ ሕግ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር SBB/72/2019 መሰረት ነው፡፡

  • መደበኛ የቁጠባ እና ኢነቨስትመንት ሒሳብ
  • አልመራህ/የሴቶች/ ቁጠባ እና ኢነቨስትመንት ሒሳብ
  • አሽባብ/የወጣቶች ቁጠባ እና ኢነቨስትመንት ሒሳብ
  • አልሚራሂቅ/የታዳጊዎች ቁጠባ እና ኢነቨስትመንት ሒሳብ
የንግድ አገልግሎቶች

የንግድ አገልግሎቶች

የንግድ አገልግሎቶች

  • በሰነድ መያዣነት የሚሰጥ ብድር /ኤል ሲ/፡-
  • የንግድ ሰነድ መሰብሰብ፡-
  • የቅድመ ክፍያ አገልግሎት
  • በአደራ መልክ የሚፈጸም ክፍያ፡-
ዲጂታል የባንክ አገልግሎት

ዲጂታል የባንክ አገልግሎት

ዲጂታል የባንክ አገልግሎት

  • በእጅ ስልክ የሚፈጸም የባንክ አገልግሎት
  • ኦንላይን የባንክ አገልግሎት
  • በኢንተርኔት የሚፈጸም የባንክ አገልግሎት
  • ሲቢኢ ብር
  • ገንዘብ መቀበያ ማሽን
  • ገንዘብ መክፈያ ማሽን

ማህበራዊ ኃላፊነት

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ800 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ። ባንኩ አጠቃላይ ሀብቱ 1 ነጥብ 1 ትሪሊዮን ብር ሀብት መድረሱንም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይህን ያስታወቀው የሀገርን ሉአላዊነት ለማስከበር ለተሰማራው መከላከያ ሰራዊትና ከፍተኛ ተሳትፎ እያደረጉ ላሉ የክልል ልዩ ኃይሎችና የአካባቢ ሚሊሺያዎች የሚያደርጉትን ተጋድሎ መደገፉን አስመልክቶ ነሀሴ 23 ቀን 2013 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው። በተገባደደው 2013 ዓ.ም በተለያዩ የባንክ አገልግሎት ዘርፎች የተሻለ አፈፃፀም የተመዘገበበት እንደነበር ያስታወቁት የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ከ140 ቢሊዮን ብር በላይ የተቀማጭ ገንዘብ መጠን በማሰባሰብ በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን ውጤት ማሳካት የቻለበት ዓመት ነበረም ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ ማኔጅመንትና ሠራተኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ620 ሺህ በላይ ችግኞችን ተከሉ።

“ኢትዮጵያን እናልብስ” በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለሶስተኛ ጊዜ በሚካሄደውና በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አነሳሽነት በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ ማኔጅመንትና ሠራተኞች በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ620 ሺህ በላይ ችግኞችን ተክለዋል። በአዲስ አበባ ከተማ በአይ.ሲ.ቲ ፓርክ ጊቢ ውስጥ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ባደረጉት ንግግር ባንኩ በደን ልማትና በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ ላለፉት አመታት በርካታ ሥራዎችን ማከናወኑን ገልጸው፣ ዘንድሮም ለሶስተኛ ጊዜ በሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር ላይ መሳተፉን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የላቀ አፈፃጸም ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶችና የሪጅን ጽ/ቤት የእውቅና ሽልማት ሰጠ::

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2020/21 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀሙን እና የ2021/22 በጀት ዓመት ዕቅዱን ላለፉት ጥቂት ቀናት ሲገመግም የቆየ ሲሆን ሀምሌ 24 ቀን 2013 ዓ.ም የማጠቃለያ መርሀ ግብር አካሂዷል፡፡ በማጠቃለያ መርሀ-ግብሩ የላቀ አፈፃጸም ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶችና የሪጅን ጽ/ቤት የእውቅና ሽልማት ተሰጥቷል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዳለፉት በርካታ ዓመታት ሁሉ የባንክ አገልግሎትን በመላ ሀገሪቱ በማስፋፋት ፣ የክፍያ ስርዓቱን በማዘመን፣ደንበኞችን መሠረት ያደረጉ ልዩ ልዩ አገልግሎቶችን በማቅረብ እና የሀገሪቱን ልማት በመደገፍ ውጤታማ አመት ማሳለፉ በማጠቃለያ መርሀ-ግብሩ ላይ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው የ2013 በጀት አመት ከ140 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ በማሰባሰብ አጠቃላይ ተቀማጩን 735 ቢሊዩን ብር አደረሰ፡፡ ባንኩ በበጀት ዓመቱ ከ20.3 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱንም አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንዳስታወቁት በአንድ አመት ብቻ 140 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ ሲሰበሰብ በባንኩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ በተመሳሳይም በአመቱ ባንኩ ካደረጋቸው እንቅስቃሴዎች ከ20 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ በማሰመዝገብ አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል፡፡ የሀገሪቱን የልማት እንቅስቃሴ በአግባቡ ለመደገፍ ወሳኝ የሆነውን የውጪ ምንዛሬ ግኝት ለማሳደግ በተደረገው ጥረትም በበጀት አመቱ ከ2.86 ቢሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ከተለያዩ ምንጮች መሰብሰብ ተችሏል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሐምሌ 01 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ወር የሚቆይ ‘‘ሐጂ ለሁሉም’’ የተሰኘ የቁጠባ ንቅናቄ አስጀመረ፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ኘሬዝዳንት ክቡር ዶ/ር ሙፍቲ ሃጅ ዑመር እድሪስ ለአንድ ወር በሚቆየው የለበይክ የቁጠባ ንቅናቄ ማስጀመሪያ ወቅት እንዳሉት ማንኛውም ሙስሊም ሐጅ ለማድረግ መቆጠብ አለበት ብለዋል፡፡ ቁጠባ የግል ህይወትን ለመቀየርም፣የተሳካለት የቢዝነስ ሰው ለመሆንም ወሳኝ ነው ያሉት ሙፍቲ ሃጂ እድሪስ ከምንም በላይ እያንዳንዱ ሙስሊም በህይወት ዘመኑ ሐጅ የማድረግ ግዴታን ለመወጣት ባንኩ በአማራጭነት ያቀረበውን የለበይክ ቁጠባ ሒሳብ በመክፈት ሳይቸገሩ ሐጅ ማድረግ ጥሩ አማራጭ ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2013 ዓ.ም የጎልፍ ጨዋታ ውድድር በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በጎልፍ ክለብ የመጫወቻ ሜዳ 3 ሺህ ችግኞች ተተክለዋል፡፡

ከኢትዮጵያ ጎልፍ ማህበር ጋር በመተባባር የተዘጋጀው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2013 ዓ.ም የጎልፍ ጨዋታ ውድድር በመካሄድ ላይ ነው፡፡ ውድድሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ አስጀምረዋል፡፡ ባንኩ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ከሚያደርጋቸው ተግባራት መካከል የህብረተሰቡን ጤና ከማስጠበቅ አንፃር ከፍተኛ ጠቀሜ ያላቸውን ስፖርታዊ ውድድሮች መደገፍ መሆኑን አቶ አቤ የጎልፍ ጨዋታ ውድድሩን ባስጀመሩበት ወቅት ተናግረዋል፡፡ የጎልፍ ጨዋታ በሀገራችን ከተጀመረ ረዘም ያለ ጊዜ ያስቆጠረ ቢሆንም በብዛት ሲዘወተር እንደማይታይ የገለጹት አቶ አቤ ስፖርቱን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባቸው ጠቁመዋል፡፡

አሁናዊ መረጃ

1950

Branchs

+38.9M

Customers

+24000

Partners

+2.5 M per day

Transactions per Month

ከኢንባ ጋር የሚሰሩ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች